አዲሱ የኮርፖሬት ግብይትና ሽያጭ መመሪያ ከመንግሥት ልማት ድርጅቶችና ሌሎች አትራፊ ድርጀቶች መነሻ በማድረግ ከኮርፖሬሽኑ ነባራዊ ሁኔታ የተዘጋጀ መመሪያ ነው::
የሕግና መመሪያ አሠራርን የተከተለ ግብይትና ሽያጭ የተጠያቂነትና ባለቤትነትን ባጠናከረ መልኩ መሠራት እንዳለበት በውይይት መድረኩ ላይ ተገልጿል።
የሚወጡ መመሪያዎች በየደረጃው ለሁሉም ክፍሎች ግንዛቤ የማሰጨበጥና የግልፅነት ሥራዎችን በመሥራት ተግባራዊነታቸውን በየሂደቱ መረጋገጥ አለባቸው።
አዲስ የተዘጋጀው መመሪያ በኮርፖሬሽኑ የቦርድ አመራር ፀድቆ በቅርብ ስራ ላይ እንደሚውል ይጠበቃል፡፡